October 30, 2024
ሲሳይ ሳህሉ
በሥራ ላይ ባለው አዋጅ ለቦርድ ተሰጥቶ የነበረው የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የመመልመል ሥልጣን፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሰጥ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቅ ሕጉ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው፣ ማክሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄደው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ነው፡፡
በ2013 ዓ.ም. ፀድቆ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዕጬ ዋና ዳይሬክተር በመገናኛ ብዙኃን ቦርድ ተመልምሎ፣ በመንግሥት አቅራቢነት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚሰየም ተደንግጓል፡፡
ይሁን እንጂ በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ ሕግ፣ ሹመቱ የሌሎች አቻ ተቋማትን ተሞክሮና ከሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ አንፃር እንዲሻሻል ታስቦ መደረጉን ያስረዳል፡፡
የማሻሻያው አስፈላጊነት በሥራ ላይ ባለው ሕግ የቦርድ አሰያየምና አወቃቀር የተንዛዛና ረዥም ሒደትን የሚከተል በመሆኑ፣ ከዘርፉ ተለዋዋጭ ሁኔታ አንፃር አብሮ የማይሄድና የባለሥልጣኑን መደበኛ ተልዕኮዎች አስቻይ ውሳኔዎችን ከመስጠት አኳያ የመፈጸም አቅሙን የሚያስተጓጉል መሆኑ ታስቦበት እንደሆነ በረቂቁ ተገልጿል፡፡
በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የተካተተው የቦርድ አባላት ስብጥር፣ ከባለሥልጣኑ የቁጥጥር ሚና ጋር በተያያዘ የጥቅም ግጭቶች የሚፈጥር ሆኖ መገኘቱ እንደ ክፍተት መታየቱ ተመላክቷል፡፡
በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የቦርድ አባላት የፖለቲካ ፓርቲ አባል ወይም ተቀጣሪ ያልሆኑ ተብሎ ቢደነገግም፣ በማሻሻያ ረቂቁ የቦርድ አባላት ለመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ቅርበትና አግባብነት ካላቸው የተለያዩ አካላትና የኅብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ እንደሚሆኑ ተጠቅሷል፡፡
የፈቃድ ወይም የምዝገባ ምስክር ወረቀት አለማደስ፣ ማገድ፣ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ ከባድ ቅጣት ወይም መሰረዝ የሚያስከትሉ የተመለከቱ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ የቦርድ ኃላፊነት የነበረ ሲሆን፣ በተሻሻለው ረቂቅ ሕግ ለባለሥልጣኑ ተሰጥቷል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወያይቶበት ለዝርዝር ዕይታ ለቋሚ ኮሚቴ በመራው በዚህ ረቂቅ ሕግ ላይ አባላት የተለያዩ አስተያየቶችን አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አባል አወቀ አዘምየ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፣ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የቦርድ አባላት ከሚመረጡባቸው መሥፈርቶች አንዱ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ወይም ተቀጣሪ ያልሆኑ በሚል የተቀመጠ ቢሆንም፣ በቀረበው ረቂቅ ሕግ ግን ይህ መሥፈርት ለምን ተሻሻለ ሲሉ ጥያቄ አቀርበዋል፡፡
‹‹ይህንን አንቀጽ መሰረዝ ማለት የሚዲያ ገለልተኝነትን አደጋ ውስጥ የሚከትና በተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት እንዲተኩ የሚያደርግ፣ የሚዲያ ምኅዳሩን የሚያጠብና ከሕዝብ ሀብትነት ወደ አንድ ፓርቲ የሚወስድ በመሆኑ ማብራሪያ ይሰጠን፤›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመሳሳይ ሌላው የኢዜማ አባል አብርሃም በርታ (ዶ/ር)፣ ከገለልተኛነት ጋር በተያያዘ አዋጁ ግልጽ አይደለም ብለዋል፡፡ በሥራ ላይ ያለው አዋጅ የፖለቲካ ፓርቲ አባል የቦርድ አባል አይሆንም ቢልም፣ በተሻሻለው ረቂቅ ግን እንዲወጣ መደረጉ ትክክል ስላልሆነ፣ በቀጣይ ተስተካክሎ እንዲቀርቡ አሳስበዋል፡፡ የቀረቡትን ጥያቄዎች የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዝርዝር እንዲወያይባቸው ተመርቶለታል፡፡
No comments yet. Be the first to leave a comment!
Silence Between the Lines
May 03, 2025
A Looming Hunger Crisis: Malnutrition Rises Amid Supply Disruptions in Ethiopia
April 26, 2025
Markets in Slump Ahead of Easter Celebrations
April 19, 2025
Reviving a Vanishing Tongue: The Return of Ge’ez
April 12, 2025
Ethiopia Reads: A Grassroots Revolution in Literacy
April 05, 2025
Trapped between poverty and peril: Ethiopia’s struggle to curb youth migration
March 29, 2025
Silenced by Techno-patriarchy
February 28, 2025
From Catcalling to Femicide: The Violence We’ve Learned to Survive
December 09, 2024
Ethiopia’s Fashion Stars Shine in Creative DNA: Ethiopia 2.0
December 03, 2024
Betrayed on Every Front: How the Law, Society, and Police Failed Tsega Belachew
November 19, 2024
New Education Bill Proposes No Student Ranking Until Grade 6: A Shift Towards Inclusive Learning
October 30, 2024
November 06, 2024
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገራዊ ምክክሩ ለተፋላሚ ወገኖች ከለላ ለመስጠትና የምክክር ውጤቶችን ለመቀበል መስማማታቸው ተገለጸ
November 06, 2024
መንግሥት ያለበትን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዕዳ ለመክፈል የ845 ቢሊዮን ብር ቦንድ አፀደቀ
October 30, 2024
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በፓርላማ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ
October 30, 2024
የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የመመልመል ሥልጣን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሆን የሚደነግግ ረቂቅ ሕግ ለፓርላማ ቀረበ
October 30, 2024
‹‹በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የፈረሱት የትግራይ ክልል ምክር ቤትና የክልሉ ካቢኔ ብቻ ናቸው›› የመቀሌ ከተማ ምክር ቤት
October 30, 2024
የከተማ መሬት ረቂቅ አዋጅ መሬት ነክ ንብረቶችን ምዝገባ የሚፈቅድ ማሻሻያ ተደርጎበት ቀረበ
© Copyright 2025 Addis News. All rights reserved.