October 30, 2024
ሲሳይ ሳህሉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ነገ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሚነሱላቸው ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጡ ታወቀ፡፡
በመስከረም 2017 ዓ.ም. መጨረሻ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የመጀመሪያ ስብሰባ፣ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ሆነው የተሰየሙት ታዬ አጽቀሥላሴ በመንግሥት የዘንድሮ ዕቅድ ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማክሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ባደረገው አራተኛ ዓመት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተላከለትን የአምስት ሚኒስትሮችን ሹመት መርምሮ አፅድቋል፡፡
ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር፣ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት ነው፡፡
በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም. ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ የቱሪዝም ሚኒስትር፣ እንዲሁም ወ/ሮ ሐና አርዓያ ሥላሴ የፍትሕ ሚኒስትር ያደረጓቸውን ተሿሚዎች ፓርላማው ተቀብሎ አፅድቋል፡፡
ይሁን እንጂ አሿሿሙና ለፓርላማው እንዲፀድቅ የቀረበበትን መንገድ በተመለከተ ከአባላቱ ጥያቄ ተነስቷል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ኢዜማ አባል አቶ ባርጠማ ፈቃዱ ባነሱት ጥያቄ፣ የሁለቱ ሚኒስትሮች ሹመት ምክር ቤቱ ሦስተኛ የሥራ ዘመኑን ከመዘጋቱ በፊት በ2016 ዓ.ም. ሰኔ ወር ላይ የተሰጠ ቢሆንም፣ እስካሁን ለፓርላማው አለመቅረቡ ከምክር ቤቱ አሠራርና ሥርዓት አንፃር መታየት አለበት ብለዋል፡፡
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባል ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ‹‹ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የፍትሕ ሚኒስትር ተደርገው ሲሾሙ የነበራቸውን የትምህርት ዝግጅት በማየት በፍትሕ ዘርፍ የተሻለ ለውጥ ያመጣሉ ብዬ እጠብቅ የነበረ ቢሆንም፣ እሳቸው ከመሾማቸው በፊት ከነበሩት ሹመኞች የተለየ ምን አደረጉ? ምን ለውጥ አመጡ?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም በሕግ ትምህርት ከአንድ ደረጃውን ከጠበቀ የውጭ ዩኒቨርሲቲ ዶክትሬት ይዘው እንደ መምጣታቸውና የአገሪቱ ትልቅ ተቋም በሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያስተምሩ ስለነበሩ ለዚህ አገር ምን ለውጥ አመጡ የሚለውም አልተገመገም ብለዋል፡፡
‹‹እኔ በግሌ ቅሬታ አለኝ፣ ለፍትሕ ሚኒስትርነት ጌዲዮን (ዶ/ር) የዕውቀት ችግር አለባቸው ብዬ አይደለም፡፡ ነገር ግን አፈጻጸማቸውን ካየነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት ሲጠይቅ የነበረውን የፍትሕ ጥማት ከማስታገስና ከማርካት ይልቅ፣ አሁንም የፍትሕ ሥርዓቱ የፖለቲካ መሣሪያ እንዲሆን አድርገዋል የሚል ወቀሳ ማቅረብ አፈልጋለሁ፤›› ብለዋል፡፡ በመሆኑም ከሥልጣን የሚነሱ ሚኒስትሮች ከተሾሙ በኋላ ምን አጉድለው እንደተነሱ፣ ምን ድክመት እንዳሳዩ? ወይም ምን ዓይነት የሥነ ምግባር ጥሰት እንዳሳዩ ሳይቀርብ አዲስ የሚተኩት ሚኒስትሮች ከእነሱ በምን እንደሚሻሉ ሳይነገር ይሾማሉ በማለት፣ ይህንን ከግልጽነትና ከተጠያቂነት መርህ አንፃር የኢትዮጵያ ሕዝብና ምክር ቤቱ ማወቅ የለበትም ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በቅርቡ በተደረገው ምርጫ አሸንፈው ፓርላማውን በ2017 ዓ.ም. የተቀላቀሉት የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠውን የሕዝብ ተወካዮችና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሥልጣንና ተግባር ጠቅሰው፣ የተወሰኑት ሚኒስትሮች ከወራት በፊት ተሹመው ወደ ሥራ መግባታቸውና ለፓርላማ በወቅቱ አለመላኩን አስታውሰዋል፡፡ ‹‹ይህ ዓይነቱ አሠራር ምክር ቤቱ ሳያፀድቅና የተሾሙት ቃለ መሃላ ሳይፈጽሙ፣ ወደ ሥራ ማስገባት ሕገ መንግሥቱን መጣስ አይደለም ወይ?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትሩ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ በክረምት ወቅት የምክር ቤት አባላት ወደ ምርጫ ክልላቸው ተሰማርተው እንደነበር፣ ምክር ቤቱ ከተከፈተ ወዲህ ደግሞ አብዛኛው አባላት የሥልጠና ፕሮግራም ላይ እንደነበሩ፣ እንዲሁም አመራሮች በተመደቡባቸው ቦታዎች ላይ የአመራር ከፍተት ቢፈጠር ከአገር ጥቅምና ከሕዝብ ጥቅም አኳያ አስፈላጊ እንዳልሆነ ታይቶ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በመነጋገርና በመግባባት የተሠራ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ተስፋዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙትን ጌዲዮን (ዶ/ር) በተመለከተ ስለቀረበው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ እንደ መሪ ፓርቲና እንደ መንግሥት ግምገማ ጌዲዮን (ዶ/ር) በተሰማሩበት በፍትሕ ዘርፍ በጣም ውጤታማ መሆናቸው ተገምግሟል ብለዋል፡፡ ‹‹ዝርዝር ነገር ሳይኖር አጠቃላይና ግምታዊ በሆነ መንገድ መፈረጁ አስቸጋሪ ስለሚሆን ሌላ ጊዜ ዝርዝር ዕውቀት ኖሮን አስተያየት ብንሰጥበት ጥሩ ነው የሚል እምነት አለኝ፤›› ብለው፣ የፍትሕ ሚኒስትር በነበሩበት ጊዜ ሰፊ የለውጥ ሥራዎችን ማከናወናቸውንና በዚህ ጅማሮ በፍትሕ ዘርፍ የሚስተዋለው የሕዝብ ጥያቄ በሙሉ ተመልሷል ማለት እንዳልሆነ ግን አስረድተዋል፡፡
No comments yet. Be the first to leave a comment!
Silence Between the Lines
May 03, 2025
A Looming Hunger Crisis: Malnutrition Rises Amid Supply Disruptions in Ethiopia
April 26, 2025
Markets in Slump Ahead of Easter Celebrations
April 19, 2025
Reviving a Vanishing Tongue: The Return of Ge’ez
April 12, 2025
Ethiopia Reads: A Grassroots Revolution in Literacy
April 05, 2025
Trapped between poverty and peril: Ethiopia’s struggle to curb youth migration
March 29, 2025
Silenced by Techno-patriarchy
February 28, 2025
From Catcalling to Femicide: The Violence We’ve Learned to Survive
December 09, 2024
Ethiopia’s Fashion Stars Shine in Creative DNA: Ethiopia 2.0
December 03, 2024
Betrayed on Every Front: How the Law, Society, and Police Failed Tsega Belachew
November 19, 2024
New Education Bill Proposes No Student Ranking Until Grade 6: A Shift Towards Inclusive Learning
October 30, 2024
November 06, 2024
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገራዊ ምክክሩ ለተፋላሚ ወገኖች ከለላ ለመስጠትና የምክክር ውጤቶችን ለመቀበል መስማማታቸው ተገለጸ
November 06, 2024
መንግሥት ያለበትን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዕዳ ለመክፈል የ845 ቢሊዮን ብር ቦንድ አፀደቀ
October 30, 2024
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በፓርላማ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ
October 30, 2024
የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የመመልመል ሥልጣን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሆን የሚደነግግ ረቂቅ ሕግ ለፓርላማ ቀረበ
October 30, 2024
‹‹በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የፈረሱት የትግራይ ክልል ምክር ቤትና የክልሉ ካቢኔ ብቻ ናቸው›› የመቀሌ ከተማ ምክር ቤት
October 30, 2024
የከተማ መሬት ረቂቅ አዋጅ መሬት ነክ ንብረቶችን ምዝገባ የሚፈቅድ ማሻሻያ ተደርጎበት ቀረበ
© Copyright 2025 Addis News. All rights reserved.